በአዲስ አበባ ከተማ ህጋዊ አሰራርን የተከተለ እና ውስን የሆነውን የመሬት ሀብት ያማከለ የመሬት ዝግጅትና ማስተላለፍ ስራ ማከናወን፤ የተጎሳቆሉ አካባቢዎችን መልሶ በማልማት የተቀናጀ የመሬት መረጃ አያያዝ እና የመሬት ባንክ ስርዓት በመዘርጋት፣ የመብት ፈጠራ ስራን በማከናወን ፍትኃዊ ቀልጣፋ እና ውጤታማ አገልግሎት መስጠት፡
በ2025 ዓም ዘመናዊ የመሬት ልማት እና አስተዳደር ስርዓት የተዘረጋበትና የላቀ አገልግሎት የሚሰጥበት እና የተገልጋይ እርካታ የተረጋገጠበት ተቋም ሆኖ ማየት።
- አሳታፊነት፣
- ግልፅነት
- ፍትሀዊነት
- የላቀ አገልግሎት መስጠት
- በኃላፊነት ስሜት መስራት
- ተጠያቂነት
❖የመልሶ ማልማት እና ወሰን ማስከበር ሥራዎችን ውጤታማነት ማረጋገጥ
❖የመሬት ዝግጅት፣ ባንክ እና ማስተላለፍ ስርዓት ውጤታማነትን ማረጋገጥ
❖የመብት ፈጠራ ስርዓትን ማሻሻል
❖የአገልግሎት አሰጣጡንና የመረጃ አያያዝ ሥርዓቱን ማዘመን